Research Center
“ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች ተብሎ ተጽፎአል”
የማቴዎስ ወንጌል 21፥13
በመላው ካናዳ የሚገኙ የኅብረቱ አባል ቤተክርስቲያናት በኮቪድ 19 ምክንያት የተጀመረው የስልክ የጸሎት አገልግሎት ቀጥሎ አሁንም በየቀኑ ከሰኞ እስከ ዐርብ በምስራቅ የሰዓት አቆጣጠር ከጧቱ 8፡00 -10፡00 ድረስ በጋራ በመጸለይ ላይ ነን፡፡
ከጁን 2025 ጀምሮ ደግሞ ዕለታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ በጋራ እየተነበበ ነው፡፡ይህ ንባብ መጽሐፍ ቅዱስን በየቀኑ በጋራ በማንበብ በዓመት አንብቦ ለመጨረስ የተዘጋጀ ነው፡፡ በዚህም በኩል ሁላችንም በጋራ ተግተን እንድንሳተፍ እናበረታታለን፡፡
ጌታ ይባርካችሁ፡፡
Gebremikael, who recently received the King Charles III Coronation Medal, adds “I truly believe that if we can all come together and work toward a common goal, we can make a difference.”
የሊበን መንገድ/ Liben Way
በቶሮንቶ ከተማ ውስጥ በማልቨርን ውስጥ “Liben Way” ተብሎ የሚታወቅ መንገድ አለ። ይህ መንገድ በ2022 ዓ.ም በአቶ ሊበን ስም የተሰየመ ሲሆን ይህም የተደረገው የTAIBU ጤና ማዕከል መጀመሪያ ዋና ዳይሬክተርና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሊበን ገብረሚካኤልን ለማክበር ነው። አቶ ሊበን ገብረሚካኤል ባለፉት 17 ዓመታት TAIBUን ለጥቁሩ ማሕበረሰብ የጤናና የልማት አካል አንዲሆን በትጋት በመስራት ከፍተኛ ዋጋ የከፈሉ ናቸው።
አቶ ሊበን ገብረሚካኤል ከ20 በላይ በኅበረተስቡ ውስጥ አዲስ ተቋቋሚ የሆኑ ድርጅቶችን — ማለትም አንደ የGOOH እና Kidy Foundation Canadaን የመሳሰሉትን ጨምሮ ከመነሻ እስከ መቋቋም ድረስ ባለው ሂደት ውስጥ በመደገፍ እጅግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡። ይህም ከኦቲዝም እንክብካቤ ጀምሮ ኢትዮጵያ ውስጥ አስከሚደረገው የትራፊክ አደጋን መከላከል የሚቻልበትን ግንዛቤና ድጋፍ አስከሚሰጠው ድርጅት ያሉትን የሚያካትት ነው። አቶ ሊበን እንደሚሉት፦ “በመጀመሪያ ደረጃ የማህበረሰብ ድርጅቶች ራሳቸውን ችለው ሲቋቋሙና አስተዋጽዖ ሲያበረክቱ ሌሎችንም ለመደገፍ የሚችል አቅም ያላቸው አካላት ሆነው ሲገኙ ከማዬት የበለጠ ትልቅ ቦታ የምሰጠውና ሚያሰደስተኝ ነገር የለም ይላሉ፡፡