በቶሮንቶ የምትገኘውን የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ላለፉት 21 ዓመታት የልጆችና የወጣቶች አገልግሎትን በታማኝነት፣ በሙሉ ትጋትና በግምባር ቀደምትነት ሲያገለግሉ የቆዩትን የፓስተር ሊንዳ የ21 አመት አገልግሎትን ማጠናቀቂያና ሽግግርን በተመለከተ የደመቀ ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡ በዚህም መሠረት January 21,2024 በቤተክርስቲያኗ ልዩ የእራት ምሽትና የምስክርነት ጊዜ ተከናውኗል ። በምሽቱ ለፓስተር ሊንዳ ልዩ ልዩ ስጦታዎች የተበረከተ ሲሆን ስለአገልግሎታቸው ፍሬ በርካታ ምስክርነት ቀርቧል፡፡ ፓስተር ሊንዳም በእግዚአብሔር ምሪት ወደ አገልግሎቱ መግባታቸውን ጊዜውም ሲደርስ አሁንም በእግዚአብሔር ምሪት ለተተኪያቸው ማስረከባቸውን ገልፀዋል። በዝግጀቱ ላይ ከቤተክርስቲያኗ አገልጋዮችና አባላት በተጨማሪ ጥሪ የተደረገላቸው የቶሮንቶ ከተማ የኢትዮጵያውያንና የኤርትራውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት መሪዎችና መጋቢዎች የተለያዩ እህት አብያተክርስቲያናት መሪዎች እንዲሁም ከፓስተር ሊንዳ ጋር ያገለገሉና ቤተሰብ የሆኑ የኪዊንስ ዌይ ቶሮንቶ ካቴድራል አባላት ተገኝተው ለበኣሉ ድምቀት ሰጥተዋል፡፡በምሽቱ ፕሮግራም ላይ የቤተክርሰቲያኗ ዋና መጋቢ ፓስተር/ዶር ኤፍሬም ላእከ ማርያም የፓስተር ሊንዳ ባልድዊንን የሕይወት ታሪክና አገልግሎት አስመልክቶ በፎቶግራፍ የተደገፈ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ የቤተከርስቲያኗ የሽማግሌዎች ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ድልነሳሁ ቸኮለ እንደዚሁ በቤተክርቲያኗ አባላት ስም የምስጋና ንግግር አድርገው የተዘጋጀውን ስጦታ አበርክተዋል፡፡ በመርሃግብሩ ላይ የነበረውን የቃልና የዝማሬ አገልግሎት ያበረከቱት ከሕጻንነት ዕድሜ ጀምረው በፓስተር ሊንዳ እየተማሩና እየተኮተኮቱ ያደጉ ወጣቶች ሲሆኑ በተለያዬ የዕድሜ ክልሉ ያሉ ልጆች በየተወካዮቻቸው አማካይነት ያቀረቡት ምስጋና በጣም ልብ የሚነካ አስደሳች ትዕይንት ነበር፡፡
የካናዳ የኢትጵያውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት በቶሮንቶ የተደረገው ይህ አስደናቂ ሽግግርና በተለይም ፓስተር ሊንዳ ባልድዊን ላለፉት 21 ዓመታት ያፈሯቸው ወጣቶች በቶሮንቶ ከተማ ብቻ ሳይሆን ወደፊት በመላው ካናዳ ከተሞች ተበትነው ለቤተክርስቲያን አጋዥ ኃይሎች እንደሚሆኑ በማመን በበዓሉ ላይ ተገኘተን የአበባ ስጦታና የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላልፈናል፡፡
Research Center
That sounds incredible! Music has a way of bringing people together for a meaningful cause, especially when it supports something as significant as acquiring a Church building. Blen Markos's song dedication program seems like it was a beautiful way to contribute to the community and the Church's goals. May God bless her and her family.
- በካናዳ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት አዲስ የአመራር አባላትን መረጠ፡፡
- በኪችነር ቤቴል የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ሁለት ተጨማሪ መጋቢዎችን ሾመች፡፡ Bethel Ethiopian Evangelical Church in Kitchener appointed two pastors
- በካናዳ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ዋና ጸሐፊ ፓስተር ዮሐንስ ተፈራ በጉባኤ ተጸልዮላቸው ኃላፊነታቸውን ተረከቡ፡፡Pastor Yohannes Tefera, General Secretary of the Union of Ethiopian Evangelical Churches in Canada, assumed his duties.
- የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት በካናዳ 30ኛ ዓመታዊ የመሪዎች ስብሰባንና የሕብረቱን ዋና ጸሐፊ አገልግሎት ማስጀመር አስመልክቶ የተዘጋጀ ልዩ ኮንፈረንስ